የፖስታ አላላክ መመሪያ
የተለያዩ ሰነዶች ለማረጋገጥ
ሀ. በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተረጋግጦ ከኢትዮጵያ ለመጡ የተለያዩ ሰነዶችን ለማረጋገጥ
ለ. ከካናዳ መንግስት ለተሰጡ የተለያዩ ሰነዶችን ለማረጋገጥ
ሀ. በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተረጋግጦ ከኢትዮጵያ ለመጡ የተለያዩ ሰነዶችን ለማረጋገጥ
(የልደት እና የጋብቻ ሰርተፊኬቶች)
መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
1. ሰነዱን መጀመሪያ ባሉበት ፕሮቪንስ በኖታሪ ፐብሊክ ማረጋገጥ፣
2. በመቀጠል ኦታዋ በሚገኘው የካናዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አረጋግጦ ማቅረብ
3. ሰነዱ በካናዳ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከተረጋገጠ በኋላ የሚከተሉትን ማሟላት
4. የታደሰ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ኮፒና የካናዳ የመኖሪያ ፈቃድ ወይም የትምህርት ፈቃድ ወይም የስራ ፈቃድ ኮፒ ማቅረብ
5. የታደሰ የትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ኮፒና የካናዳ ፓስፖርት ወይም የካናዳ ዜግነትን የሚያሳ መታወቂያ ካርድ ማቅረብ
6. (ለንብረትና ፍርድ ቤት ነክ የሆኑ ሰነዶችን ለማረጋገጥ) ክፍያው የታደሰ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ወይም የትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ላላቸው $81.84 የካናዳ ዶላር ነው፡፡
7. የሌላ አገር ዜጋ ለሆኑ/በትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ የሌላቸው/አገልግሎቱ የፀና የኢትዮጵያ ፓስፖርት የሌላቸው / አገልግሎቱ የፀና የኢትዮጵያ ፓስፖርት የሌላቸው (ለንብረትና ፍርድ ቤት ነክ የሆኑ ሰነዶችን ለማረጋገጥ) $125.40 የካናዳ ዶላር ይፈጽሙ
8. ማንነትን የሚገልጽ የካናዳ ፓስፖርት ወይም የካናዳ መኖሪያ ፈቃድ ኮፒ ወይም መንጃ ፈቃድ ወይም ሌላ ተመሳሳይ መታወቂያ ካርድ ያቅርቡ፣
10. ክፍያው ለኢትዮጵያ ኤምባሲ የተጻፈ፡-
Urgent Notice to all our esteemed customers,
Please note that there is minor change of price on the various visa and document authentication services that the Embassy is providing starting from Friday September 06, 2019.
Give us a call and find out more before you send us documents until we share with you the details.
With kind regards!
በካናዳ ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሙሉ
=====================================
የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ከተቋቋመ ወዲህ የመጀመሪያው የሆነው የዲያስፖራ በዓል ኦገስት 2019 መጨረሻ ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች ማለትም፡-
• ከዲያስፖራ ምሁራን ጋር በቅንጅት የተዘጋጀ ስልጠናና ሲምፖዚየም፣
• ከውጭ የሚመጡ የዳያስፖራ የቢዝነስ ሰዎችና በአገር ውስጥ በቢዝነስ ከተሰማሩ ሰዎች ጋር የቢዝነስ ለቢዝነስ ውይይት( B2B) እና
• በአገር ውስጥ በኢንቨስትመንት እና ቢዝነስ የተሰማሩ የዳያስፖራ ድርጅቶች የቢዝነስ ውጤቶችን የሚያሳይ ኤግዚብሽን በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሂዳል።
ስለሆነም፣ በካናዳ አገር የምትገኙ እንዲሁም በአገር ቤት በኢንቨስትመንት እና በቢዝነስ የተሰማራችሁ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሚካሄደው
የዲያስፖራ በዓል ላይ እንድትሳተፉ ኤጀንሲው ግብዣውን ያስተላለፈ በመሆኑ ለመሳተፍ የምትፈልጉ እስከ ጁላይ 21/ 2019 ድረስ
በስልክ ቁጥር (613) 565 6637 Ext 213 ወይም በኢሜል አድራሻ info@ethioembassycanada.org፣
merga.tufa@ethioembassycanada.org ወይም fiseha.zerihun@ethioembassycanada.org
መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን።
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ
ኦታዋ
በክቡር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች የተላለፈ መልዕክት
በውጭ አገራት የምትኖሩ ወጣት ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባላችሁ የክረምት ዕረፍት ጊዜ በአገር ቤት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት መስክ እንድታገለግሉና የወደፊቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት የበኩላችሁን የማይተካ ሚና እንድትጫወቱ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን መልዕክት ተላልፏል፡፡
ስለሆነም፣ በዚህ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለመሳተፍ የምትፈልጉ ወጣቶች በኤምባሲው በኩል በአካል በመቅረብ፣ በስልክ ቁጥር(613) 565 6637(የውስጥ መስመር 213) እና (613) 565 6637(የውስጥ መስመር 204) በመደወል እና በኢሜል አድራሻ merga.feyisa@ethioembassycanada.org እና fiseha.zerihun@ethioembassycanada.org ፍላጎታችሁን በመግለጽ እንድትመዘገቡ እያስታወቅን፣ መንግስት እናንተን በተቀደሰ ተግባር ላይ ለማሰማራት አስፈላጊውን ዝግጅት ያደረገ መሆኑን እንገልጻለን።
የኢትዮጵያ ኤምባሲ
ኦታዋ፣ ካናዳ
ሰኔ ፣ 2011 ዓ.ም.
የቅጥር ማስታወቂያ
በሞንትሪያል (ካናዳ) የሚገኘው የዓለም አቀፍ ሲቪል አቪየሽን ድርጅት (ICAO) የኢትዮጵያ ተወካይ ጽ/ቤት በስራ ቀናት በጠዋት ሺፍት ብቻ ለማሰራት አንድ የጽ/ቤት ፀሐፊ (Administrative Assistant) በኮንትራትበካናዳ ነዋሪ ከሆኑ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መካከል አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ለተጠቀሰው ክፍት የስራ ቦታ ለመወዳደር የምትፈልጉ ከዚህ በታች በሰፈሩት መስፈርቶች መሠረት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
አስፈላጊ መስፈርቶችና የምዝገባ ሁኔታ፡-
ወይም፣ በዓለም አቀፍ ሲቪል አቪየሽን ድርጅት (ICAO) የኢትዮጵያ ተወካይ ጽ/ቤት፣ 999 Robert
Bourassa Boulevard; Suite 8.40.49; Montreal, Quebec H3C 5J9
ከዚህ በላይ የተመለከቱትን መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከየካቲት 26 ቀን 2011 ዓ.ም. (March 5/2019) ጀምሮ ካሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ (ከመጋቢት 3-16 /March 12-25) መረጃችሁን በመያዝ በአካል ኦታዋ በሚገኘው የኢፌዲ.ሪ. ኤምባሲ ወይም በዓለም አቀፍ ሲቪል አቪየሽን ድርጅት (ICAO) የኢትዮጵያ ተወካይ ጽ/ቤት ወይም በኢ-ሜይል፡- info@ethioembassycanada.orgእና Ethiopia@icao.int ወይም በፖስታ በመላክ መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡ ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 613-565-6637 ext 213ወይም 514-954-6664/5775 መደወል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ኤምባሲ
ኦታዋ
በካናዳ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት በአሁኑ ወቅት በአገራችን በመካሄድ ላይ ካለው ለውጥና ዲያስፖራው በአገሩ ጉዳይ የበለጠ ተሳትፎውን እንዲያሳድግ በሰጠው ትኩረት የዲያስፖራ ጉዳዮችን የሚመራው የስራ ክፍል ከፍ ብሎ ራሱን ችሎ በኤጀንሲ ደረጃ እንዲዋቀር አድርጓል፡፡ ይህ አዲስ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ በይፋ ስራ ለማስጀመር በተለያዩ አገሮች የሚገኙ የዳያስፖራ ተወካዮች በስነ ስርዓቱ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል፡፡
ስለዚህ እ.ኤ.አ ማርች 1 ቀን 2019 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚካሄደው የ Launching ስነ ስርዓት ላይ ከካናዳ ሁለት የራሳቸውን የትራንስፖርትና ሌሎች ወጪዎችን በመሸፈን ለመሳተፍ ፍላጎት ያላችሁ የኮሙኒቲ አባላት በኦታዋ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ በስልክ ቁጥር 613-565-6637 Ext. 203 ወይም Ext. 204 በመደወል ወይም በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የኢፌዲሪ ኤምባሲ
ኦታዋ ካናዳ
INFORMATION REGRDING THE DIASPORA TRUST FUND
Invitation for Bid
Name of Country: Ethiopia
Name of Project: Procurement of 400,000 MT wheat grain or milling wheat for Ministry of Trade and Industry (Ethiopian Trading Business Corporation).
Procurement Reference number: PPPDS/ETBC/ICB/PG/131/03/2011
(a) Documents will be issued at Ministry of Finance, compound No.2, block 5th, 1stfloor, room No. 101, Telephone 011-1-540524, 011-1-223755/22
(b) Bids must be delivered to, and will be opened at PPPDS, Ministry of Finance, compound No.2, Block No. 5th, 1st floor conference Hall.
PPPDS reserves the right to reject any or all bids and any items on the bid.
Public Procurement and Property Disposal Service (PPPDS)
Tel. 011-1-540524, 011-1-223755 or 011-1-223722
Website; http://www.pppds.gov.et
Addis Ababa, Ethiopia
ለውድ ተገልጋዮቻችን በሙሉ፡-
ኤምባሲያችን በፓስፖርት፣ ቪዛና የሰነድ ማረጋገጫ አገልግሎቶች ላይ ባለው የምንዛሪ ልዩነት የዋጋ ለውጥ ያደረገ መሆኑን እየገለጸ አገልግሎቶቹንና የዋጋ ዝርዝር በተመለከተ በድኅረ ገጻችን Consular Section በሚለው ሜኑ ስር የምታገኙ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ
ኦታዋ ካናዳ
ለሁሉም ኢትዮጵያዊያንና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን
በካናዳ በጉዲፈቻ መንገድ የመጡ ህፃናትና ወጣቶች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ሚሲዮናችን እነዚህን ዜጎች በማግኘትና ፍላጎት ያላቸውን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማገናኘት እንዲሁም ያሉበትን ሁኔታ ኤምባሲው ለማወቅና ለመደገፍ ስለፈለገ ይህ መረጃ እንዲደርሳቸውና አድራሻቸውን እንድታሳውቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
ስልክ ቁጥር (613) 565 6637 ext 204፣ 207፣ 213
ወይም በኢሜል፡ info@ethioembassycanada.org
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ኤምባሲ ኦታዋ
Announcement
For all types of Visas /ለሁሉም ዓይነት የቪዛ ጥያቄ /
Use online E-Visa:
https://www.evisa.gov.et/#/home
Announcement [ለውድ ተገልጋዮች!!]
ጉዳዩ፡ የውክልና ሰነዶችን የማረጋገጥ አገልግሎት አሰራር ላይ የተደረገ ለውጥን ይመለከታል፡፡
ከዚህ ቀደም አገልግሎቱ ያላበቃ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ወይም አገልግሎቱ ያላበቃ የትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ለያዛችሁ ተገልጋዮች ያዘጋጃችሁትን ውክልና ኖታሪ [ Notary] በማድረግ ብቻ ወደ ኤምባሲያችን በመላክ የማረጋገጥ ስራ ስናከናውን መቆየታችን ይታወቃል፡፡ ሆኖም ከሰኔ 14 ቀን 2010 ዓ/ም [ ከጁን 21/2018] ጀምሮ ማንኛውም ወደ ኤምባሲያችን የሚላኩ ኖታሪ [ Notary] የተደረጉ የውክልና ሰነዶች ወደ ኤምባሲያችን ከመላካቸው በፊት እንደሌሎች ሰነዶች ኦታዋ በሚገኘው የካናዳ ግሎባል አፌየርስ [ Canadian global Affairs in Ottawa ] ከተረጋገጡ በኋላ ወደ ኤምባሲያችን መላክ እንደሚኖርባቸው በአክብሮት መግለጽ እንወዳለን፡፡በሌላ በኩል የውክልና ሰነድ መስጠት ለሚፈልጉ ቫሊድ የሆነ የኢትዮጵያ ፓስፖርትና ትውልደ ኢትዮጵያ መታወቂያ ያላቸው ተገልጋዮች ኤምባሲው ጽ/ቤት በአካል ቀርበው ሰነዱ ላይ በመፈረም በቀላሉ አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ቆንስላ አገልግሎት
ለበለጠ መረጃ እባክዎ www.ethioembassycanada.org ይጎብኙ፡፡
EMBASSY OF ETHIOPIA
WASHINGTON DC, USA
ETHIOPIAN CONSULATE GENERAL
LOS-ANGELES, LA, USA
ETHIOPIAN MISSION TO THE UN
NEW YORK, USA
MINISTRY OF FOREIGN AFFAIRS
ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Embassy Address:
1501-275 Slater Street, Ottawa Ontario
K1P 5H9 Canada
Tel (613) 565 6637 / Fax (613) 565 9175
Email: info@ethioembassycanada.org
For consular services
Email: consular@ethioembassycanada.org