የፖስታ አላላክ መመሪያ
የተለያዩ ሰነዶች ለማረጋገጥ
ሀ. በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተረጋግጦ ከኢትዮጵያ ለመጡ የተለያዩ ሰነዶችን ለማረጋገጥ
ለ. ከካናዳ መንግስት ለተሰጡ የተለያዩ ሰነዶችን ለማረጋገጥ
ሀ. በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተረጋግጦ ከኢትዮጵያ ለመጡ የተለያዩ ሰነዶችን ለማረጋገጥ
(የልደት እና የጋብቻ ሰርተፊኬቶች)
መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
መጀመሪያ ለማረጋገጥ የሚፈለገው ሰነድ በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያቤት ተረጋግጦ ማቅረብ
2. የአገልግሎት ክፍያ መጠን
· የታደሰ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ወይም የትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ኮፒ
በማቅረብ $ 77.88 የካናዳ ዶላር ክፍያ ይፈፅሙ።
· የሌላ አገር ዜጋ ለሆኑ/በትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ የሌላቸው/ አገልግሎቱ
የፀና የኢትዮጵያ ፓስፖርት የሌላቸው $ 118.80 የካናዳ ዶላር ክፍያ ይፈፅሙ።
3. ክፍያው ለኢትዮጵያ ኤምባሲ የተፃፈ፡-
· መኒ ኦርደር /Money Order/ ወይም
· ሰርቲፋይድ ባንክ ቼክ /Certified Bank Check/
4. ሰነዱን በፖስታ ቤት በኩል የሚልኩ ከሆነ ፣ አድራሻዎ የተጻፈበት መመለሻ ፓስታ
Tracking Number ያለው FEDEX ወይም UPS ወይም ቅድሚያ የተከፈለበት አስቸኳይ ወይም
የተመዘገበ የካናዳ ፖስታ መሆን ይገባዋል፡፡
ለ. ከካናዳ መንግስት ለተሰጡ የተለያዩ ሰነዶችን ለማረጋገጥ
መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
1. ሰነዱን መጀመሪያ ባሉበት ፕሮቪንስ በኖታሪ ፐብሊክ ማረጋገጥ
2. በመቀጠል ኦታዋ በሚገኘው የካናዳ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አረጋግጦ ማቅረብ
3. የአገልግሎት ክፍያ መጠን (ለንብረትና ፍርድ ቤት ነክ የሆኑ ሰነዶችን ለማረጋገጥ)
· የታደሰ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ወይም የትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ኮፒ
በማቅረብ $ 81.84 የካናዳ ዶላር ክፍያ ይፈፅሙ።
· የሌላ አገር ዜጋ ለሆኑ/በትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ የሌላቸው፣እና
አገልግሎቱ የፀና የኢትዮጵያ ፓስፖርት የሌላቸው $ 125.40 የካናዳ ዶላር ክፍያ ይፈፅሙ።
4. ክፍያው ለኢትዮጵያ ኤምባሲ የተፃፈ፡-
· መኒ ኦርደር /Money Order/ ወይም
· ሰርቲፋይድ ባንክ ቼክ /Certified Bank Check/
5. የመጠየቂያ ቅጽ መሙላት (click here to download a form)
6. ሰነዱን በፖስታ ቤት በኩል የሚልኩ ከሆነ ፣ አድራሻዎ የተጻፈበት መመለሻ ፓስታ
Tracking Number ያለው FEDEX ወይም UPS ዋወይም ቅድሚያ የተከፈለበት
አስቸኳይ ወይም የተመዘገበ የካናዳ ፖስታ መሆን ይገባዋል፡፡
INFORMATION REGRDING THE DIASPORA TRUST FUND
Invitation for Bid
Name of Country: Ethiopia
Name of Project: Procurement of 400,000 MT wheat grain or milling wheat for Ministry of Trade and Industry (Ethiopian Trading Business Corporation).
Procurement Reference number: PPPDS/ETBC/ICB/PG/131/03/2011
(a) Documents will be issued at Ministry of Finance, compound No.2, block 5th, 1stfloor, room No. 101, Telephone 011-1-540524, 011-1-223755/22
(b) Bids must be delivered to, and will be opened at PPPDS, Ministry of Finance, compound No.2, Block No. 5th, 1st floor conference Hall.
PPPDS reserves the right to reject any or all bids and any items on the bid.
Public Procurement and Property Disposal Service (PPPDS)
Tel. 011-1-540524, 011-1-223755 or 011-1-223722
Website; http://www.pppds.gov.et
Addis Ababa, Ethiopia
ለውድ ተገልጋዮቻችን በሙሉ፡-
ኤምባሲያችን በፓስፖርት፣ ቪዛና የሰነድ ማረጋገጫ አገልግሎቶች ላይ ባለው የምንዛሪ ልዩነት የዋጋ ለውጥ ያደረገ መሆኑን እየገለጸ አገልግሎቶቹንና የዋጋ ዝርዝር በተመለከተ በድኅረ ገጻችን Consular Section በሚለው ሜኑ ስር የምታገኙ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ
ኦታዋ ካናዳ
ለሁሉም ኢትዮጵያዊያንና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን
በካናዳ በጉዲፈቻ መንገድ የመጡ ህፃናትና ወጣቶች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ሚሲዮናችን እነዚህን ዜጎች በማግኘትና ፍላጎት ያላቸውን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማገናኘት እንዲሁም ያሉበትን ሁኔታ ኤምባሲው ለማወቅና ለመደገፍ ስለፈለገ ይህ መረጃ እንዲደርሳቸውና አድራሻቸውን እንድታሳውቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
ስልክ ቁጥር (613) 565 6637 ext 204፣ 207፣ 213
ወይም በኢሜል፡ info@ethioembassycanada.org
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ኤምባሲ ኦታዋ
Announcement
For all types of Visas /ለሁሉም ዓይነት የቪዛ ጥያቄ /
Use online E-Visa:
https://www.evisa.gov.et/#/home
Announcement [ለውድ ተገልጋዮች!!]
ጉዳዩ፡ የውክልና ሰነዶችን የማረጋገጥ አገልግሎት አሰራር ላይ የተደረገ ለውጥን ይመለከታል፡፡
ከዚህ ቀደም አገልግሎቱ ያላበቃ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ወይም አገልግሎቱ ያላበቃ የትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ለያዛችሁ ተገልጋዮች ያዘጋጃችሁትን ውክልና ኖታሪ [ Notary] በማድረግ ብቻ ወደ ኤምባሲያችን በመላክ የማረጋገጥ ስራ ስናከናውን መቆየታችን ይታወቃል፡፡ ሆኖም ከሰኔ 14 ቀን 2010 ዓ/ም [ ከጁን 21/2018] ጀምሮ ማንኛውም ወደ ኤምባሲያችን የሚላኩ ኖታሪ [ Notary] የተደረጉ የውክልና ሰነዶች ወደ ኤምባሲያችን ከመላካቸው በፊት እንደሌሎች ሰነዶች ኦታዋ በሚገኘው የካናዳ ግሎባል አፌየርስ [ Canadian global Affairs in Ottawa ] ከተረጋገጡ በኋላ ወደ ኤምባሲያችን መላክ እንደሚኖርባቸው በአክብሮት መግለጽ እንወዳለን፡፡በሌላ በኩል የውክልና ሰነድ መስጠት ለሚፈልጉ ቫሊድ የሆነ የኢትዮጵያ ፓስፖርትና ትውልደ ኢትዮጵያ መታወቂያ ያላቸው ተገልጋዮች ኤምባሲው ጽ/ቤት በአካል ቀርበው ሰነዱ ላይ በመፈረም በቀላሉ አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ቆንስላ አገልግሎት
ለበለጠ መረጃ እባክዎ www.ethioembassycanada.org ይጎብኙ፡፡
EMBASSY OF ETHIOPIA
WASHINGTON DC, USA
ETHIOPIAN CONSULATE GENERAL
LOS-ANGELES, LA, USA
ETHIOPIAN MISSION TO THE UN
NEW YORK, USA
MINISTRY OF FOREIGN AFFAIRS
ADDIS ABABA, ETHIOPIA
Embassy Address:
1501-275 Slater Street, Ottawa Ontario
K1P 5H9 Canada
Tel (613) 565 6637 / Fax (613) 565 9175
Email: info@ethioembassycanada.org
For consular services
Email: consular@ethioembassycanada.org